የዲሲ ሰባዊ መብቶች ቢሮ/ OHR /የፌብሯሪ ወርሃዊ ጋዜጣ - የዳይሬክተሩ መልዕክት
ፌብሪዋሪ ወር ከሌሎቹ ወራቶች አጭር ወር ሊሆን ይችላል፣ ነገር ግን በዚህ አመት ትልቅ ትርጉም አለው። ከአንድ መቶ ዓመት በፊት የታሪክ ምሁር እና ደራሲ ዶ/ር ካርተር ጂ. ዉድሰን የጥቁር ታሪክ ፈጽሞ እንዳይረሳ ለማድረግ እንቅስቃሴ አነሳስቷል። ዛሬ የጥቁር ህዝቦች ታሪክ መታሰቢያዎችን የአንድ ምዕተ ዓመት የጥቁር ታሪክ መታሰቢያ ስናከብር ያንን ቃል ኪዳን ወደፊት እናስቀጥላለን፣ እንዲሁም የጥቁር አሜሪካውያንን ታሪኮች፣ ድሎች እና መስዋዕቶች እንገነዘባለን። ከንቲባ ቦውዘር እንዳስታወሱን “የዲሲ ታሪክ የጥቁሮች ታሪክ ነው።” በመሆኑም ያንን ታሪክ መጠበቅና ማስተላለፍ የእያንዳንዱ ትውልድ ኃላፊነት መሆኑን እናውቃለን።
ዶ/ር. የዉድሰን ራዕይ በፌብሩዋሪ 1926 ብሔራዊ የማሰላሰል ጊዜን ፈጥሯል፣ ፕሬዝዳንት ጄራልድ ፎርድ በ1976 የጥቁር ታሪክ ወርን በይፋ እውቅና ሰጥተው አሜሪካውያን “በታሪካችን ውስጥ በሁሉም ዘርፎች ጥቁር አሜሪካውያንን ችላ የተባሉትን ስኬቶች የማክበር እድልን እንዲጠቀሙ” ጥሪ አቅርበዋል።
የዘንድሮው በዓል በሐዘን የታጀበ ነው፤ ድምፃቸውና ድፍረታቸው የዲስትሪክቱንና የሀገራችንን የሞራል ገጽታ ያጠናከሩትን የሲቪል መብቶች ተሟጋችነትን በማሳየት ረገድ ከፍተኛ ሚና የተጫወቱትን የቄስ ጄሲ ጃክሰንን ሞት የዘከርን ነው። ብዙ ጊዜ “በፍርሃትና በመከፋፈል ወደ ኋላ ሳይሆን በተስፋ ወደፊት መሄድ አለብን” ሲል ያሳስበናል፤ ይህ መልእክት ዛሬም በተለይ አጣዳፊ ሆኖ ይሰማናል። ቄስ አል ሻርፕተን የጃክሰንን ሞት ሲያስቡ፣ ሁኔታውን እንደሚከተለው አስፍረውታል "ዛሬ እናዝናለን" ግን አንሸሽም። የጃክሰን ቤተሰብ የተለከሰውን ችቦ እንዲረከብና እእንዲይዝ እንጸልያለን። ቄስ ጄሲ ጃክሰንን ለማክበር ትልቁ መንገድ በማስታወስ ብቻ ሳይሆን በእንቅስቃሴ ነው። ሰልፉን እንድናስቀጥል አስተምሮናል። መደራጀታችንን እንድንቀጥል አስተምሮናል። ፍትህ በፍፁም እንደማይሰጥ እንደሚጠየቅ አስተምሮናል።
ይህንን መንፈስ በአእምሯችን ይዘን ቢሮአችን በአገሪቱ ውስጥ ካሉት እጅግ ተራማጅ የሲቪል መብቶች ሕጎች አንዱ የሆነው የዲሲ የሰብአዊ መብቶች ሕግ ዛሬ በከተማችን ውስጥ ያለውን ተሟጋችነት እንዴት እንደሚቀርጽ እና እንደሚያነቃቃ ትርጉም ያለው ውይይት እያካሄደ ነው። ይህ ውይይት የተለያዩ እውቀቶችን እና የህይወት ተሞክሮዎችን ያካተቱ የፓናል አባላትን ያካተተ ሲሆን ዲስትሪክቱን ለሁሉም የበለጠ ፍትሃዊ ከተማ ወደመሆን ለማቅናት ስንሰራ አብረን ልንጋፈጣቸው የሚገቡንን ወሳኝ ጥያቄዎች ይዳስሳል። ለበለጠ መረጃ ከታች ያለውን በራሪ ወረቀት ይመልከቱ እና በውይይቱ ለመሳተፍ ይመዝገቡ።
በዚህ ወር መጀመሪያ ላይ ከከንቲባዋ የዜጎች ጉዳዮች ቢሮ ጋር በመተባበር ተጨማሪ የቢሮ የስራ ሰዓቶችን አድርገን መስራት ጀምረናል፣ ይህም እስከ ማርች ድረስ የሚቀጥል ይሆናል። ተደራሽነትን ማስፋት እና የማህበረሰብ አባላት ባሉበት ቦታ መገናኘት ለኤጀንሲው ዋና ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ ነው። ተጨማሪ ዝርዝሮችን ከታች ባለው በራሪ ወረቀት ላይ ማግኘት ይችላሉ፣ እንዲሁም በከተማዋ ውስጥ ባሉ አጎራባች ሰፈሮች ውስጥ የሚኖሩ ተጨማሪ የስራ ሰዓቶችን እንዲከታተሉ እናበረታታዎታለን።
የጥቁር አሜሪካውያንን የአንድ ምዕተ ዓመት የጥቁር ታሪክ መታሰቢያ ስናከብር እና የጥቁር አሜሪካውያንን አስተዋጽኦ ስናከብር፣ ከፊታችን የተደቀነውን ኃላፊነት እንቀበላለን፤ ይህም ቀደም ሲል የነበሩትን ትውልዶች ሥራ፣ እድገት እና ድፍረት ለማስቀጠል ነው። ይህ ቃል ኪዳን ለአንድ ወር ብቻ የተወሰነ ሊሆን አይችልም። ወደ ፍትህና እኩልነት የሚወስደው መንገድ ቀጣይነት ያለው መሆኑን እና ትርጉም ያለው ለውጥ የሚቻለው በዓላማና በተስፋ አብረን ወደፊት ስንራመድ መሆኑን በየቀኑ የምናስታውስ መሆን አለበት።
ይህንን ሥራ ወደፊት ለማራመድ - በተሳትፎ፣ በአጋርነት እና ለቤተሰቦቻችን፣ ለጎረቤቶቻችን እና ለማህበረሰቦቻችን የበለጠ አካታች የሆነች ዲሲን ለመገንባት በጋራ ቁርጠኝነት - OHRን እንዲቀላቀሉ እጋብዝዎታለሁ።
በአጋርነት፣
Elizabeth Fox-Solomon

